Tuesday, September 10, 2013

የ2005 የጊዜ መሥመር


በማሕሌት ፋንታሁን

ክቡራት የዞን 9 ነዋሪዎች ዓመቱ ከማለቁ በፊት እንዴት እንዳለፈ ለማስታወስ እንዲረዳን በማሰብ በ2005 የተከናወኑ አበይት ተግባራትን በዓመቱ የጊዜ መሥመር ላይ እንደሚከተለው ለማሳየት ሞክረናል፡፡ መልካም አዲስ ዓመት ይሁንላችሁ፡፡

መስከረም
  • §  መስከረም 11/2005 የተከበሩ ኃ/ማርያም ደሳለኝ የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ሆነው፣ የተከበሩ ደመቀ መኮንን ደግሞ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነው ቃለ መሐላ ፈፀሙ፣
  • §  መስከረም 17 ቀን 2005 ድምፃዊ ቴድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) በሒልተን ሆቴል አንድ ሺሕ ያህል ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት ጋብቻውን ፈፀመ፣

ጥቅምት
  • §  ጋዜጠኛ ርዕዮት ዓለሙ አሜሪካን ሃገር ከሚገኘው የዓለም አቀፉ የሴቶች ሚዲያ ፋውንዴሽን የ2012 ‹ፅናት በጋዜጠኝነት ሥራ› የተሰኘ ሽልማት አገኘች፣
  • §  የ2005 የእስልምና ምክር ቤት /መጅሊስ/ ምርጫ በየቀበሌው ተካሄደ፣  

Thursday, September 5, 2013

#EthiopianDream: Yes, I also have a Dream!

By Zelalem Kibret
 
Half a century ago one of the great personalities of the 20th century, Dr. Martin Luter King Jr. declare his dream to his America and fellow black citizens of that nation. Three months before Dr. King’s Washington declaration, here in Africa the Organization of African Unity (OAU) was established in Addis Ababa, Ethiopia.

The OAU’s choice of Ethiopia as a head quarter is not an accidental decision; rather it is recognition to Ethiopia’s symbolic status in the heart and minds of Black peoples. Ethiopia defeats European conquerors and able to resist the Scramblers of Africa. The black world who is subjugated, conquered and enslaved by sort water invaders takes this Ethiopia’s resistance as a symbol of defiance and Ethiopia itself as a beacon of Freedom.

But, Fifty Years later the symbolic OAU establishment, the black world is still not free. Ethiopia’s bravery and resistance of foreign colonizers seems in vain to establish a JUST Ethiopia. Because Ethiopia, dreamed by the black world as an inspiration is:

A land of Injustice,
A Land of Inequality,
A symbol of Famine and Hunger,
A land of hopeless wonderers,
A forgotten hellish corner of the world…

Even if Ethiopia inspires many to pursuit their freedom and rights, Ethiopia put a yoke of oppression to its citizens. Ethiopia hangs the bell of Freedom afar. Ethiopia ranks its citizens as first class and second class. Ethiopia built the wall of tyranny and dictatorship that becomes a noise to humanity. The Ethiopia that fence itself with fire to protect its sovereignty set its citizens in a fire ablaze within.

Wednesday, September 4, 2013

Press Release for the Fourth Online Campaign “Ethiopian Dream – Let us all dream it together”


Zone9 is an informal group of young Ethiopian activists and bloggers working together to create an alternative independent narration of the socio-political conditions in Ethiopia and thereby foster public discourse that will result in emergence of ideas for the betterment of the Nation. 

In an effort to meet our objectives, we have conducted three different online campaigns that we believe have informed citizens and called for good governance. The fourth and last of the Ethiopian year 2005 campaign will be held under the motto “Ethiopian Dream – Let us all dream it together” between 5th-7th of September, 2013. 

Our country Ethiopia is home of rich history, beautiful cultures and identities. Having and recognizing our differences, the presence of an all-inclusive shared national dream is a crucial element in the nation building effort. It is in this view that the 4th online campaign will try to create a stage for all Ethiopians to envision a better Ethiopia. 

Among the major objectives of the campaign are: · 

a) to envision an all-inclusive country, equal to Ethiopians from all walk of life and background and accommodative of all cultures and identities, 

b) to seek for ways that encourage and look for just economic, social and political progress in the country, 

c) to preach for religious tolerance and 

d) to envision Ethiopia that all Ethiopians aspire to live in and none desire to leave behind. 

The campaign mainly will be held on Twitter and Facebook. Articles, that motivate citizens to question themselves and discuss their dream for the country, will be published on our blog. Status updates and tweets (containing unique hashtag #EthiopianDream is developed for the purpose) will be circulated. Banners will be developed to be used as a profile picture throughout the campaign period.

Dear all Ethiopians who want to see Ethiopia an even more proud nation that is equal to all, where citizens work together focusing on human and national development without any negative feeling for each other; you all are invited to join the campaign to sharing your dream and sharing others’ dream. 

Zone9 
We blog because we care!!!

የአራተኛው የበይነመረብ ዘመቻ ጋዜጣዊ መግለጫ - “ኢትዮጵያዊ ሕልም፤ ኑ አብረን እናልም!”


ዞን 9 ኢ-መደበኛ የአራማጆች እና የጦማሪያን ቡድን ኢትዮጵያ ውስጥ ስላለው ማኅበረሰባዊ እና ፖለቲካዊ ሁኔታ የተለየ እና ወገናዊ ያልሆነ ተረክ ለመፍጠር እየሰራ የሚገኝ የወጣቶች ስብስብ ነው፡፡ ይህንን የምናደርግበት ዋና አላማ ሁሉም ኢትዮጵያውያን የሀገሪቷ ጉዳይ ያገባኛል ብለው ውይይት የማድረግ ባህል እንዲያሳድጉ በማድረግ ሀገሪቷን በሁሉም መስኮች ወደተሻ ለደረጃ የሚያደርሱ ሃሳቦች እንዲወለዱ ለማመቻቸት ነው፡፡ 

የተከበራችሁ የዞን9 ነዋሪዎች፣ በ2005 ዓ.ም ሊደረጉ ከታቀዱት አራት የበይነ መረብ ዘመቻዎች አራተኛው እና የመጨረሻው ዘመቻ ነገ ሐሙስ ነሐሴ 30 ቀን 2005 ዓ.ም እስከ ቅዳሜ ጳጉሜን 2 ቀን 2005 ዓ.ም ድረስ ይካሄዳል፡፡ አራተኛው ዘመቻ ‹‹#ኢትዮጵያዊ_ሕልም፤ ኑ አብረን እናልም!›› በሚል ርዕስ መላው ኢትዮጵያውያንን ኢትዮጵያ ሆና ማየት የሚፈልጉትን እና እዚያ ለመድረስ መደረግ አለበት የሚሉትን የሚያካፍሉበት ይሆናል፡፡ 

የረጅም ታሪክ፣ የውብ ባሕል እና ማንነቶች ባለቤት በሆነችው ሀገራችን ኢትዮጵያ፤ ዜጎቿ እርስ በርስ ተስማምተው እና ሁሉንም ዕኩል ባሳተፈ መልኩ ሀገሪቷን ለመገንባት ከሚያስችሉት ግብዓቶች መሐከል የጋራ ሕልም መኖሩ ዋነኛው ነው፡፡ ይህንኑ ታሳቢ በማድረግ አራተኛው የበይነመረብ ዘመቻ ኢትዮጵያዊያን ለኢትዮጵያ ያላቸውን የወደፊት ተስፋ እንዲጋሩ መድረክ ለመፍጠር ይጥራል፡፡ 

የዘመቻው ዋና ዓላማዎችም፤ ሁሉንም አካታች፣ ለሁሉም ምቹ፣ ለሁሉም ዕኩል ዕድል የምትሰጥ ኢትዮጵያን ለማመለካከት፣ የቋንቋ እና ባሕላዊ ኅብርን አስፈላጊነት እና ጥቅም ለማመላከት፣ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ፍትሕን ለማምጣት የሚበጁ አመለካከቶችን ለማስረጽ፣ ሃይማኖታዊ መቻቻልን ለመስበክ እና በተለይም ሁሉም ኢትዮጵያዊ ሊኖርባት የሚፈልጋት፣ ተሰዶ የማይወጣባት፣ ከሰሜን እስከ ደቡብ፣ ከምስራቅ እስከ ምዕራብ ያሉ ኢትዮጵያውያን ሁሉ ዕኩል የሚታዩባት፣ የሚጠቀሙባት እና የሚጠቅሟት ኢትዮጵያን ማለም እንዲቻል ማድረግ ይሆናሉ፡፡

ዘመቻው በዋነኛነት የሚካሄደው ‹‹ፌስቡክ›› እና ‹‹ትዊተርን›› በመጠቀም ይሆናል፡፡ ዜጎች ለሀገሪቷ ያላቸውን ሕልም በተመለከተ እራሳቸውን እንዲጠይቁ እና እንዲወያዩ የሚያስችሉ የተለያዩ ጽሑፎች በጦማራችን ይወጣሉ፡፡ በሁለቱ ማኅበራዊ አውታሮች ላይ ለዚሁ ዘመቻ ሲባል የተዘጋጁ አጫጭር ጽሑፎች ይሰራጫሉ፡፡ ዘመቻውን የሚመለከት ‹ባነር› ተዘጋጅቶ ዘመቻው በሚቆይባቸው ቀናት የተለያዩ ፕሮፋይል ምስሎችም ተዘጋጅተው የሽፋን ምስል እና የፕሮፋይል ፎቶ ይሆናሉ፡፡

ኢትዮጵያ ለሁሉም ዜጎቿ ምቹ፣ ሁሉም ዜጎቿ ካለምንም የጥላቻ ስሜት እርስ በርስ ተደጋግፈው ሰብኣዊና ቁሳዊ የሀገር ግንባታ ላይ ብቻ የሚያተኩርበት እና የበለጠ የምታኮራ ሀገር ሆና ማየት የምትፈልጉ ኢትዮጵያውያን ሁሉ በዚህ ዘመቻ የነቃ ተሳትፎ በማድረግ ሕልማችሁን እንድታጋሩ እና የሌሎችን ሕልም እንድትጋሩ እንጋብዛለን፡፡

ስለሚያገባን እንጦምራለን!!! 
ዞን9